“በውኃ ድርሻ ላይ መግባባት ባለመኖሩ 4ኛው ዙር የህዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቅቋል” የህዳሴ ግድብ ተደራዳሪ ቡድን መሪ አምባሳደር ስለሽ በቀለ

46

ባሕር ዳር: ታኅሳሥ 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ዋና ተዳራዳሪው አምባሳደር ስለሽ በሰጡት መግለጫ የህዳሴ ግድብ ድርድር ባለፈው የኢትዮጵያ ግብፅ መሪዎች በተስማሙበት መሰረት ለ4ተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ተካሒዶ ያለስምምነት መጠናቀቁን ጠቅሰዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለአካባቢው ዋነኛ የውኃ ቋት መኾኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ነው ያሉት።

የህዳሴ ግድብ ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በድርቅ ጊዜ በሚኖር የውኃ አያያዝ እና አለቃቅ ላይ መሰረት ያደረገ ድርድር መደረጉን ያነሱት አምባሳደር ስለሽ በድርድሩ መርሆች ስምምምነት አንቀፅ 6 ላይ ግብፆች በውኃ ድርሻ ክፍፍል ላይ መደራደር ባለመፈለጋቸው ድርድሩ ያለስምምነት ተቋጭቷል ብለዋል።

በአንዱዓለም መናን

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ከባሕር ዳር – ወልዲያ ያለውን የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት በዚህ ዓመት አጠናቅቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየሠራን ነው” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
Next articleየሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ውሳኔዎችን አሳለፈ።