
ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 06/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሠው አልባ የአየር ምድብን መርቀው ከፈቱ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከሠዓት መርሐ ግብር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን እጩ መኮንኖች፣ የአውሮፕላን ጥገና ሙያተኞችን እና ፓይለቶችን እንደሚያስመርቁ ይጠበቃል።
88ኛው የኢትዮጵያ አየር ኀይል የምስረታ በዓል በልዩ ልዩ ዝግጅቶቾ እየተከበረ መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት ገጽ መረጃ ያመላክታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
