ባለስልጣኑ የጎንጂ-ቆለላን ጨምሮ አራት የመንገድ ፕሮጀክቶችን ውል ተፈራረመ፡፡

479

ባሕር ዳር፡ የካቲት 12/2012 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አራት የመንገድ ፕሮጀክቶችን የውል ስምምነት ከተቋራጭ ድርጅቶች ጋር ዛሬ ተፈራርሟል፡፡

የጎንጂ-ቆለላ (ቆሬ-አዲስ አለም)፣ የግሸን መገንጠያ ዲዛይንና ግንባታ፣ የቆሼ-ሚጦ-ወራቤ እንዲሁም የጋምቤላ-አቦቦ-ዲማሎት የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቶች ውል ነው የተፈረመው።

ኢ.ፕ.ድ እንደዘገበው በፊርማ ስነ ስርአቱ ላይ መንገዶቹ ከሚሰሩባቸው አካባቢዎች የተወከሉ የሀገር ሽማግሌዎችና የአስተዳደር አካላት ተገኝተዋል።

Previous articleየእቴጌ ጣይቱ ብጡል መታሰቢያ ሃውልት በደብረ ታቦር ከተማ ሊገነባ ነው፡፡
Next articleወጥነት ያለው የማረም እና የማነጽ መተዳደሪያ ደንብ መዘጋጀቱን ኮሚሽኑ አስታወቀ፡፡