
ባሕር ዳር: ኅዳር 29/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የብሔር፣ ብሔረሰቦችን ቀን ምክንያት በማድረግ ፕሬዚዳንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ ጅግጅጋ ዛሬ ማለዳ ላይ ጅግጅጋ ገብተዋል።
ጅግጅጋ ሲደርሱም በሶማሊ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሙስጠፋ ሙሐመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የክልል እና የፌዴራል የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከሶማሊ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!