
ባሕር ዳር: ኅዳር 28/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ትምህርት ሚኒስቴር የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ምደባን ይፋ አደረገ።
በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የ”ሪሚዲያል” ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባቸውን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
ተማሪዎች የተመደቡበት የትምህርት ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ”ሪሚዲያል” ፕሮግራሙን እንዲከታተሉም አሳስቧል።
ሚኒስቴሩ የተማሪዎችን የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
ተማሪዎች የተመደቡበትን ተቋም ለመመልከት ከታች የቀረቡትን አማራጮች መጠቀም ይችላሉ፡-
Website: http://Result.ethernet.edu.et
Telegram : https://t.me/moestudentbot
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!