የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦችን ቀን ለማክበር ርእሳነ መሥተዳድሮችና ከንቲባዎች ጂግጂጋ ገቡ።

34

ባሕር ዳር: ኅዳር 28/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የተለያዩ ክልሎች ርእሳነ መሥተዳድሮች እና የሁለቱ ከተማ አሥተዳደሮች ከንቲባዎች በኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል ላይ ለመታደም ጂግጂጋ ከተማ ገብተዋል፡፡

ርእሳነ መሥተዳድሮቹና ከንቲባዎቹ ጂግጂጋ ሲገቡ የሶማሌ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሙስጠፌ መሐመድና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“እንኳን ለኢትዮጵያዊነት በዓል አደረሳችሁ” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
Next articleየአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆነ።