18ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በጅግጅጋ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡

37

ባሕር ዳር: ኅዳር 26/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በዓሉ ዛሬ ህዳር 26/2016 ዓ.ም የብዝኃነት ቀን በሚል ስያሜ በልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች በደማቅ ኹኔታ እንደሚከበር በኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ተረፈ በዳዳ አስታውቀዋል::

የበዓሉ አካል የኾነው የባሕል ኤግዚቢሽን ትናንት መከፈቱ ይታወሳል። የኢግዚቢሽኑ መከፈት በርካታ ዓላማዎች እንዳሉትም አቶ ተረፈ እንዲህ አብራርተዋል፡፡

📕 ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዝኃነት ተምሳሌት መኾኗን ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ሀገራት ማሳየት

📕 የብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች ባሕልን በማስተዋወቅ የባሕል ልውውጥ እና የሕዝቦች ትስስርን ማጎልበት፤ እርስ በርስ እንዲተዋወቁ እድል መፍጠር

📕 ያደገ ትውውቅን በማረጋገጥ መቻቻልን፣ መከባበርን እና አብሮነትን ማረጋጥ

📕 ኅብረ-ብሔራዊነት ላይ የተመሰረተ ሀገራዊ አንድነት ግንባታን ማጎልበት

📕 ኢትዮጵያዊ ማንነት ማለት የሁሉም የብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች ማንነት፣ ባሕል እና እሴቶች ድምር ውጤት መኾኑን ማሳየት ናቸው ተብሏል።

ዘጋቢ፡- አብነት እስከዚያ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleዳር 15/2016 ም.አ ቺርቤዋ ጋዚቲ
Next articleነገስ ምን እንኾን ይኾን?