“የኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀል ከሩሲያ ጋር ያላትን ትብብር ያጠናክራል” ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን

53

ባሕር ዳር: ኅዳር 25/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏ ከሩሲያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክረው መኾኑን የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ገለጹ።

በሩሲያ ፌዴሬሽን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ቻም ኡጋላ ኡሪያት የሹመት ደብዳቤያቸውን ለሩሲያው ፕሬዝዳንት አቀርበዋል ፡፡

አምባሳደሩ የሹመት ደብዳቤያቸውን ባቀረቡበት ወቅት ፕሬዝዳንት ፑቲን ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያና ሩሲያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከመሰረቱ 125 ዓመታትን ያስቆጠሩ ወዳጅ አገራት መኾናቸውን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በሩሲያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በማድረግ የተለያዩ የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸው ግንኙነቱን ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዳሻገረው መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል።

ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏ ደግሞ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በኦስትሪያና ቼክ ሪፐብሊክ ያደረጉት ቆይታ እንዲሁም በኮፕ 28 የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ የነበራቸው ተሳትፎ ስኬታማ ነበር” ቢልለኔ ስዩም
Next articleከ120 ሺህ በላይ የኾኑ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት እንዲያገኙ ማድረጉን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡