በትምህርት ዘርፉ የሚደረገው የማሻሻያ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ተባለ።

62

ባሕር ዳር: ኅዳር 18/2016 ዓ.ም (አሚኮ)32ኛው የትምህርት ጉባኤ በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በእውቀት የበለጸገ ዜጋ ለመፍጠር በትምህርት ዘርፉ የሚደረገው የማሻሻያ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።

ሚኒስትሩ ባለፉት ሁለት ዓመታት በትምህርት ዘርፉ የተሰራው ሥራ ያለንበትን ደረጃ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነበር ብለዋል።

በትምህርት ሥርዓቱ እየተደረገ ያለው ማሻሻያ ብቁ ዜጎችን ለመፍጠር እድል የሚሰጥ ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ የተደረገው የማሻሻያ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleባለፉት አራት ወራት ከ193 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።
Next articleበሕፃናት ስብዕና ግንባታ ላይ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ተጠየቀ።