በሻንጋይ ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድል ቀንቷታል፡፡

36

ባሕር ዳር: ኅዳር 15/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በሻንጋይ ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሥራነሽ ይርጋ አሸንፋለች፡፡ አትሌቷ 2:21:28 በኾነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቃለች።

አትሌት ሥራነሽ ይርጋ ዳኜን በመከተል ኬንያዊቷ አትሌት ሴሊ ቼፕየጎ ካፕቲች 2:21:55 በኾነ ሰዓት በመግባት ሁለተኛ ኾና አጠናቅቃለች።

በወንዶች ኬኒያዊው አትሌት ፊሊሞን ኪፕቱ ኪፕቹምባ 2:05:35 በኾነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቅቋል። ታንዛኒያዊው አትሌት አልፎንስ ሲምቡ 2:05:39 በኾነ ሰዓት በመግባት በአራት ሰከንድ ልዩነት ውድድሩን ሁለተኛ ኾኖ አጠናቅቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየባሕር ዳር ከተማ አሥተዳዳር ለ820 ባለይዞታዎች የመሬት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር መሥጠቱን አስታወቀ፡፡
Next articleበ13ተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ።