
ደሴ: ኅዳር 11/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በኮምቦልቻ ከተማ የሳር መንደር የመኖሪያ ፕሮጀክት ግንባታ የሶማሌ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሙስጦፋ መሐመድ በተገኙበት መሰረተ ድንጋይ ተቀመጠ።
ርእሰ መሥተዳድር ሙስጦፋ በቢራሮ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የሳር መንደር የቤቶች ግንባታ በባለሃብቶች ለመገንባት ጥረት መጀምሩ አንዳችን ለሌላችን የአብሮነታችን ማሳያ ነው ብለዋል። በቀጣይም ባለሃብቶች በየአካባቢያቸው ያሉ በአኢኮኖሚ አቅማችው ዝቅተኛ የሆኑ ዜጎችን መደገፍ ያስፈልጋል ብልዋል።
ርእሰ መስተዳድሩ በኮምቦልቻ ከተማ ልዩ ልዩ የመሰረተ ልማት ሥራዎችንም ጎብኝተዋል።
ዘጋቢ:- ደጀን አምባቸው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!