ከተማ አሥተዳደሩ በተቀናጀ የኅብረተሰብ ተሳትፎ የልማትና የመልካም አሥተዳደር ሥራዎችን በትኩረት እንደሚሠራ ገለፀ።

40

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 07/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በጎንደር ከተማ አሥተዳደር በየደረጃው ያሉ መሪዎች በቀጣይ በአንድ ወር በኅብረተሰቡ ተሳትፎ በሚከናወኑ እቅዶች ዙሪያ ተወያይተዋል ።

ለውይይቱ ተሳታፊዎች መነሻ ፅሁፍ ያቀረቡት የከተማ አሥተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ እንደገለፁት አሁን በከተማዋ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም በመጠቀም በኅብረተሰቡ ተሳትፎ የልማትና የመልካም አሥተዳደር እቅዶችን ለማከናወን በትኩረት ይሠራል ።

በቀጣይ ትኩረት ከሚሰጥባቸው ተግባራት መካከል በኢኮኖሚው ዘርፍ የተጀመሩ መሠረተ ልማቶችን ማጠናቀቅ ፣ የግብርናና የእንሰሳት ሀብት ፣ ገቢ ማሰባሰብ ፣የሥራ እድል ፈጠራ ሥራዎች በትኩረት ይሠራሉ ሲሉ ከንቲባው ተናግረዋል ።
ከተማ አሥተዳደሩ በማህበራዊ ዘርፍ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል ፣የወባ በሽታ ስርጭትን መከላከል ትኩረት የሚሰጣቸው ተግባራት መሆናቸውን አስታውሰዋል ።

ከመልካም አሥተዳደር ሥራዎች አኳያ ደግሞ የዋጋ ማረጋጋት ሥራዎች ማከናወን ፣ የማኅበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከል ሥራዎችን ማከናወን የመንግሥት ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል ትኩረት የተሰጣቸው እቅዶች መሆናቸውን ከንቲባው ገልጸዋል ።

በከተማ አስተዳደሩ ለሚከናወኑ ለታቀዱ እቅዶች ለማሳካት የተቀናጀ የኅብረተሰብ ተሳትፎ ማሳደግ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል ።

እቅዶችን ለማሳካትም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች በትኩረት መስራት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ አሳስበዋል ።

የፖለቲካና የሕዝብ ግንኙነት ሥራዎችን አስመልክቶ የመወያያ ፅሁፍ በጎንደር ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋ መኮንን ቀርቧል።

የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ሥራዎችን በተገቢው መንገድ መሠራት እንደሚገባ አቶ ተስፋ ተናግረዋል ።

መረጃው የጎንደር ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየጀርመኑ ዩኒየን በርሊን ክለብ በሀገሪቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት አሠልጣኝ መሾሙን አስታወቀ።
Next article“ያሉንን ሰፊ አቅሞች እና የጋራ የልማት ግቦች ስናጤን ደቡባዊው ዓለም ለደቡብ-ደቡብ የኢኮኖሚ ትብብር መጎልበት ታላቅ አቅም እንዳለው እንረዳለን” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)