“በውይይትና በመግባባት እንጂ በአፈሙዝ የሚፈታ የሕዝብ ጥያቄ የለም” የደሴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ አባላት

39

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 06/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የደሴ ከተማ አሥተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የመንግሥት ሠራተኛ መሰረታዊ ድርጅት ኮንፈረንስ አካሂደዋል፡፡

ኮንፈፍረንሱ እየተገኘ ያለውን ሰላም በማፅናት ላይ የመሠረታዊ ድርጀት አባላቱ ስለሚኖራቸው ሚና እና በቀጣይ የ90 ቀናት የፓርቲ ሥራዎች ዕቅድ ላይ በትኩረት መክሯል፡፡ የተጀመረውን የአመራር ሪፎርም ሥራ በማጠናከር ጥራት ያለው

አመራር በአመለካከትና በተግባር የመገንባቱ ሥራ ስለማጠናከርና የአባላቱ ሚና ምንነት ላይ በውይይቱ በስፋት ተነስቶ ምክክር ተደርጎበታል። በውይይትና በመግባባት እንጂ በአፈሙዝ የሚፈታ የሕዝብ ጥያቄ ባለመኖሩ በሁሉም ችግሮቻችን ዙሪያ በመወያየት በተቀመጠው የመፍትሔ አቅጣጫ ላይ በጋራ መሥራት እንደሚጠበቅም ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡ መረጃው የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ነው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበ2 ቢሊዮን ዶላር ወጭ የአገልግሎት ማስፋፊያ እንደሚያደርግ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገለጸ።
Next article“ደረጃቸውን የጠበቁ የትምሕርት ተቋማትን መገንባት ብቁ የኾነ የሰው ኃይልን ለማፍራት የላቀ አስተዋጽኦ አለው” ምክትል ርእሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን