ኢትዮጵያ ከጂቡቲ እና ሶማሊያ ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሄደች።

69

ባሕር ዳር: ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ኢትዮጵያ ከሳውዲ – አፍሪካ ጉባዔ ጎን ለጎን ከጂቡቲ እና ሶማሊያ ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከሳዑዲ – አፍሪካ ጉባዔ ጎን ለጎን ከጂቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ እና ከሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼህ ሞሃመድ ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት ከሳዑዲ – አፍሪካ ጉባዔ ጎን ለጎን ከወንድሞቼ የጂቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ እና የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼህ ሞሃመድ ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአማራ ክልል ከ376 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ልማት እና ጥበቃ ሥራ ይከናወናል።
Next article“የምንወዳትን ሀገራችንን ለሚቀጥለው ትውልድ ለማስተላለፍ ኢትዮጵያዊ አብሮነትን ማስቀደም ይገባል” አቶ ይርጋ ሲሳይ