ሳዑዲ የኢትዮጵያን የልማት ሥራዎች እንደምትደግፍ አስታወቀች።

41

ባሕር ዳር: ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ሳዑዲ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን እንደምትደግፍ አረጋግጣለች፡፡

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ከሳዑዲ አቻቸው መሐመድ አል ጅዳን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ውይይቱ በሪያድ እየተካሄደ ከሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ- አፍሪካ ኢኮኖሚ ኮንፍረንስ ጎን ለጎን ነው የተደረገው፡፡

በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ ልማት እና እዳ ሽግሽግ ላይ መምከራቸውን በሳዑዲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየመጀመሪያው ሀገራዊ የሳይበር ደኅንነት ጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።
Next articleባሕር ዳር ከተማ እንግዶቿን እየተቀበለች ነው።