
ባሕር ዳር: ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ከተማ የሚካሄደውን የ3ኛ ዙር የአመራሮች ሥልጠና ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራው መጠናቀቁ ተገልጿል።
የብልጽግና ፓርቲ የዲሞክራሲ ባሕል ግንባታ ዘርፍ ኀላፊ መለስ ዓለም፣ የብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ እና የባሕር ዳር ሥልጠና አስተባባሪዎች የሥልጠና ማዕከሎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ከተማዋ እና የሥልጠና ማዕከሎችም ቀድመው ዝግጁ ስለመኾናቸውም ተናግረዋል። የ3ኛው ዙር የአመራር ሥልጠና በአማራ ክልል በባህር ዳር፣ ጎንደር እና ደሴ ከተሞች ይካሄዳል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!