የኢትዮጵያ ከ15 ዓመት በታች ወንዶች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ዩጋንዳ አቀና።

61

ባሕር ዳር: ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም (አሚኮ)የኢትዮጵያ ከ15 ዓመት በታች ወንዶች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ዩጋንዳ አቀንቷል።

ውድድሩ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት ከጥቅምት 24 እስከ ህዳር 6 ይካሄዳል። የሴካፋ ከ15 ዓመት በታች ውድድር ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ታዳጊ ቡድን በምድብ ሀ ከአስተናጋጇ ዩጋንዳ ፣ ኢትዮጵያ ፣ ጅቡቲ እና ደቡብ ሱዳን ጋር ተደልድሏል። ዛሬ ለውድድሩ ቡድኑ ወደ ዩጋንዳ ጉዞ መጀመሩን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከቅርጫት ኳስ ተጫዋችነት እስከ ዝነኛ የዓለም ዋንጫ ዳኛነት
Next articleለክብራቸው መታሰቢያ፣ ለታሪካቸው መዘከሪያ”