በሦስት ወራት ከዳያስፖራው ከ745 ሺህ ዶላር በላይ ድጋፍ ተሰብስቧል” የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት

75

ባሕር ዳር: ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ሦስት ወራት ከዳያስፖራው ከ745ሺ ዶላር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት አስታውቋል።

አገልግሎቱ እንደገለጸው በበጀት ዓመቱ ሩብ ዓመት በሬሚታንስና በኢንቨስትመንት የተገኘውን ሀብት ሳይጨምር ከ745 ሺህ በላይ ዶላር ድጋፍ ተልኳል፡፡

ለዓባይ ግድብ ከቦንድ ሽያጭ ፣ ከስጦታና ከልዩ ልዩ ፕሮግራሞች ከ93 ሺህ ዶላር በላይ ማሰባሰብ ተችሏል፡፡

ለገበታ ለትውልድ ፕሮጀከትም ከ163 ሺህ ዶላር በላይ ማሰባሰብ መቻሉም ተገልጿል።

ለልዩ ልዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ከ488 ሺህ ዶላር በላይ በጥሬ ገንዘብና በአይነት ድጋፍ መገኘቱን ኢፕድ ዘግቧል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በምሥራቅ ጎጃም ዞን አንፃራዊ ሰላምና መረጋጋት በተፈጠረባቸው ወረዳዎች ትምህርት ተጀምሯል” የዞኑ ትምህርት መምሪያ
Next articleየሲቢኢ ኑር ከወለደ ነጻ የባንክ አገልግሎት ራሱን የቻለ የመንግሥት ባንክ እንዲኾን የባንኩ የሼሪዓ አማካሪ ምክር ቤት አባላት ጠየቁ።