ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የልማት ሥራዎችን ለመገምገም እና የበጋ ስንዴ ልማት ሥራን ለማስጀመር አፋር ክልል ተገኝተዋል።

70

ባሕርዳር፡ ጥቅምት 17/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካን ቡድናቸው ጋር በመኾን የልማት ሥራዎችን ለመገምገም እና የበጋ ስንዴ ምርት ሥራን ለማስጀመር አፋር ክልል ተገኝተዋል::

በዱብቲ ወረዳ ኅብረተሰቡ በ8ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የበጋ ስንዴ ለማምረት ተዘጋጅቷል::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በያዝነው ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ በ3 ሚሊዮን ሔክታር ላይ የበጋ ስንዴ ለማምረት አቅደናል ብለዋል ::

በዋነኝነት በአርብቶ አደርነት የሚታወቀው እና በግብርና ግብዓቶች የቀዳሚ ድጋፍ መዳረሻ ያልሆነው የአፋር ክልል በአኹኑ ወቅት በሀገር አቀፉ የግብርና ምርታማነት ላይ በስንዴ በጥጥ በሙዝ ምርት አስተዋፅኦው እጅግ ከፍ እያለ መጥቷል:: መረጃው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ነው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየቱሪዝም ዘርፉ በየጊዜው በሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች እየፈተነ እንደሚገኝ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
Next articleየማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ምስረታ የማጠቃለያ መርሐ-ግብር በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።