ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ.ር) በግብርና ዘርፍ ኢንደስትሪን ማዕከል ያደረገ ልማት እንዲጠናከር ጥሪ አቀረቡ ።

24

ባሕርዳር፡ ጥቅምት 07/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በግብርና ዘርፍ ትብብርን ማስፋት ብሎም ኢንዱስትሪን ማእከል ያደረገ ልማትን ማጠናከር እንደሚገባ በመግለጽ ጥሪ አቅርበዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ.ር) የዕለቱ ውሎ ሁለተኛ መርሐ-ግብር በ3ኛው ቢአርአይ ከፍተኛ ጉባዔ ላይ “Connectivity in an Open Global Economy” በሚል ጭብጥ ንግግር ማቅረብ ነበር።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባዔው በኢትዮጵያ የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭን ስኬታማ ልምድ አጋርተዋል::

በግብርና ዘርፍ ትብብርን ማስፋት ብሎም ኢንዱስትሪን ማእከል ያደረገ ልማትን ማጠናከር እንደሚገባም ጥሪ ማቅረባቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የኑሯችን መሰረት የኾነውን የደረጃዎች ጥራት በመተግበር ሁሉም ኀላፊነቱን ሊወጣ ይገባል” የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት
Next articleየአማራ ክልል ጤና ቢሮ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር የዓለም የዕይታ ቀንን አስመልክቶ የዓይን ህክምና አገልግሎት ሰጠ