6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ጉባዔ መካሄድ ጀመረ።

42

ባሕርዳር፡ መስከረም 28/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የ6ኛው ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት የኢፌዴሪ ፕሬዘዳንት በተገኙበት ዛሬ ተከፍቷል።

የኢፌዴሪ ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች አባላት በተገኙበት የፌደራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ እያቀረቡ ይገኛሉ።

በምክር ቤቱ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት የሁለቱ ምክር ቤቶች አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች፣ የክልል ርእሰ መሥተዳድሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 5ቱ ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ችለዋል” ትምህርት ሚኒስቴር
Next article“በተለወጠ ሀሳብ እና በተለወጠ ልቦና ልንነሳ ይገባል” ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ