ፋሲል ከነማ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቋል።

39

ባሕር ዳር: መስከረም 26/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ፋሲል ከነማ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዓመቱ የመጀመሪውን ጨዋታ ከሃዋሳ ከነማ ጋር አድርጎ በአቻ ውጤት አጠናቋል።

ዓጼዎቹ በመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ለእረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተው ነበር።

ከእረፍት መልስ ሃዋሳ ከነማዎች በተከታታይ ሦስት ግቦችን ከመረብ አገናኝተው ፋሲልን 3 ለ 2 መምራትም ችለው ነበር።

በመጨረሻም የዓጼዎቹ የመሃል ሜዳ ተጫዋች ሱራፌል ዳኛቸው በጨዋታው ለራሱ ሁለተኛ ለቡድኑ ደግሞ ከሽንፈት የታደገችውን ግብ አስቆጥሮ ጨዋታው ሦስት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበስምንተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜር ሊግ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ወደ አሸናፊነት ተመለሰ።
Next articleበቱርክ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው።