የኢሬቻ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል ገለጸ።

14

የኢሬቻ በዓል የገዳ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ በሰላም መከበሩን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል አስታውቋል፡፡

አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገራችንና ከጎረቤት ሀገራት የመጡ እንግዶች እና ቱሪስቶች የታደሙበት የኢሬቻ በዓል በሰላም እና በልዩ ድምቀት መከበሩን ነው የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ያስታወቀው፡፡ የበዓሉ በሰላም መከበር የሀገሪቱን መልካም ገፅታ ለመገንባት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ግብረ-ኃይሉ ጠቅሷል። በዓሉ ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከበር የድርሻቸውን ለተወጡ ሁሉ ግብረ-ኃይሉ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

Previous articleየኢሬቻ በዓልን አብሮነትና ወንድማማችነትን በሚያጠናክር መልኩ በድምቀት ማክበራቸውን አባ ገዳዎችና የበዓሉ ታዳሚዎች ተናገሩ።
Next article“በ190 ቀበሌዎች የወባ መከላከያ ኬሚካል ርጭት ሊካሄድ ነው” የአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት