‹‹በማንኛውም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚፈጸምን ግፍ እናወግዛለን!›› የጎንደር ከተማ አሥተዳድር ሠላማዊ ሰልፈኞች

415

የጎንደር ከተማ አሥተዳድር ነዋሪዎች በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የተፈጸመውን የእገታ ድርጊት እያወገዙ ነው፡፡

ከደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወጥተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱ እገታ የተፈጸመባቸው ተማሪዎች ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የጎንደር ከተማ አሥተዳድር ነዋሪዎች እየጠየቁ ነው፡፡

መንግሥት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሠራ፣ ህግንም እንዲያስከብር ነው በሰላማዊ ሰልፉ እየጠየቁ የሚገኙት፡፡

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ እያስተላለፏቸው ከሚገኙት መልዕክቶች መካከል ‹‹በማንኛውም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚፈጸምን ግፍ እናወግዛለን፤ የሀሰትና የፈጠራ ታሪኮች ይከልከሉ፤ በአማራ ሕዝብ ላይ ሚፈጸመው ግፍና በደል በአስቸኳይ ይቁም፤ በዩኒቨርሲቲ የአማራ ተማሪዎች ላይ የሚፈጸመው ግፍ በአስቸኳይ ይቁም!›› የሚሉት ይገኙበታል፡፡

ፎቶ፡- በእመቤት ሁነኛው እና በኃይሉ ማሞ

Previous article80ኛ ዓመት የሰባት ቤት አገው ፈረሰኞች ማኅበር የፈረሰኞች ትርዒት-በእንጂባራ
Next articleየጎንደር ከተማ ተማሪዎች ለታገቱት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድምጻቸውን እያሰሙ ነው፡፡