17

የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ይቀጥላሉ።

ባሕር ዳር: መስከረም 23/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ሁለተኛ ዙር ጨዋታዎችን እያከናወነ ያለው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ከ ምድብ 5 እስከ 8 የሚካሄዱ ጨዋታዎችን ያስተናግዳል።

የአምናው የዋንጫ ባለቤት ማንቸስተር ሲቲ ወደ ጀርመን ተጉዞ አርቢ ሊፒዚንግን የሚገጥምበት መርሐ ግብር ትልቅ ግምት ተሰጥቶታል።

ሌላኛው የእንግሊዝ ተወካይ ኒውካስል ዩናይትድ ከፈረንሳዩ ፒ ኤስ ጂ፣ የጀርመኑ ቦርሲያ ዶርትመንድ ከጣሊያኑ ኤሲ ሚላን የሚያደርጓቸው ጨዋታዎችም ተጠባቂ ናቸው። የስፔኑ አትሌቲኮ ማድሪድም የሆላንዱን ፌየኖርድ በሜዳው ያስተናግዳል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በመካከላችን የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሰከነ ውይይት መፍታት ይገባል” የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች
Next articleየክልሉ ሰላም እየተሻሻለ መምጣቱን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አስታወቁ።