ብልሹ አሠራርን የማይጠየፍ አመራርን እንደማይታገስ የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።

44

ደብረ ብርሃን፡ መስከረም 23/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ምክርቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት 39ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን አከናውኗል።

በጉባዔው ላይ የከተማ አሥተዳደሩ ተቀዳሚ ከንቲባ በድሉ ውብሸት ለወቅታዊው የሰላም እጦት እና ቀውስ ብልሹ አሠራርና አሉታዊ ተፅዕኖው የገዘፈ ነው ብለዋል።

ተቀዳሚ ከንቲባው በሥነ ምግባር የታነፀ የአገልጋይነት መንፈስ ያለው የሥራ ኀላፊ እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡

ጉባኤው ለ 20 የከተማው የሥራ ኀላፊዎች ሹመት በመስጠት ተጠናቋል።

ዘጋቢ፡- ዮናስ ታደሰ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የሴፍቲኔት መርሐ ግብር ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከማድረጉ ባሻገር ለከተማው ልማት አዎንታዊ ድርሻ እየተወጣ ነው” የጎንደር ከተማ አሥተዳደር
Next article“ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳይመጡ የሰላሙ ኹኔታ እክል ፈጥሯል” የደቡብ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ