
ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ዛሬ በላቲቪያ ሪጋ በተካሄደው የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ በላቲቪያ ሪጋ በተካሄደው የዓለም የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በ5 ኪሎ ሜትር የሴቶች ውድድር አትሌት እጅጋየሁ ታዬ እና መዲና ኢሳ ሦስተኛ አራተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።
በውድድሩ የወርቅና ብሩን ሽልማት ቢያትሪስ ቺቤት እና ሊሊያን ካሳይት ከኬንያ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን ይዘው ውድድሩን አጠናቅቀዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!