የድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ሐውልት ተመረቀ።

146

ባሕር ዳር: መስከረም 17/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ልክ የዛሬ ዓመት በድንገት ሕይወቱ ያለፈው የዝነኛው ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ የአንደኛ ዓመት መታሰቢያ በተለያዩ ዝግጅቶች እየታሰበ ነው::

ዛሬ ማለዳ የድምፃዊው ቤተሰቦች፣ የሙያ አጋሮች እና አድናቂዎች በተገኙበት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን የማዲንጎ ሐውልት ተመርቋል::

ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር ቆይታ ያደረገው የማዲንጎ የሙያ ባልደረባ አርቲስት ብርሀኑ ተዘራ በቀጣይ በድምፃዊው ተጀምረው የተጠናቀቁ የሙዚቃ ሥራዎች ለአድማጭ እንደሚቀርቡ ገልጿል::

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“እንጎሮጎባሽ ”
Next article“ዛሬም በዓለም የተደበቀ ሰላም አለ፤ እሱን እንደ መስቀሉ ፈልገን ማግኘት አለብን” የዋግኽምራ ሀገረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖደስ አባል ብፁዕ አቡነ በርናባስ