ሰላማዊ ሰልፎቹ በሠላም መጠናቀቃቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

236

በደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የተፈጸመውን እገታ ለማውገዝ የተካሄዱ ሠላማዊ ሰልፎች በሠላም መጠናቀቃቸውን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

 የእገታ ድርጊቱን እና በጉዳዩ ላይ የመንግሥትን ዝምታ በማውገዝ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ሠላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ ተማሪዎቹ ተለቅቀው ከወላጆቻቸው ጋር እንዲገናኙ፣ ኢ-ሰብዓዊ እና ከሞራል ያፈነገጠውን ድርጊት የፈጸሙት አካላትም ተጠያቂ እንዲሆኑ በሠልፎቹ ተጠይቋል፡፡

በኮሚሽኑ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር መሠረት ደባልቄ ለአብመድ እንደገለጹት በሁሉም አካባቢዎች የተካሄዱ ሰልፎች በሠላማዊ መንገድ ተጠናቅቀዋል፡፡ የየአካባቢው ማኅበረሰብ፣ ወጣቶች እና የጸጥታ አባላት ሠላማዊ ሰልፎች በሠላማዊ መንግድ እንዲጠናቀቁ  ላደረጉት ጥረት ኮሚሽኑ አመሥግኗል፡፡

ዘጋቢ፡- ዳግማዊ ተሠራ

Previous article“የአጋቾችን ማንነት፣ ያገቱበትን ምክንያት እና እንዴትና ለምን ታገቱ? የሚለውን ጉዳይ ለማወቅ ከፍተኛ የምርመራ ቡድን ተዋቅሮ በቅንጅት እየተሠራ ነው፡፡” የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን
Next articleየታገቱ ተማሪዎችን በተመለከተ መንግስት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የምሁራን መማክርት ጉባኤ በድጋሜ ጠየቀ፡፡