
ባሕር ዳር: መስከረም 15/2015 ዓ.ም (አሚኮ)በ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት ከ22 ሺህ በላይ የሥራ ዕድል ለመፍጠር አቅዶ እየሠራ እንደኾነ የደብረብርሃን ከተማ አሥተዳደር ሥራ እና ሥልጠና መምሪያ አስታውቋል።
የመምሪያው ኀላፊ ብዙዓየሁ ሰይድ የሥራ እድል የሚፈጠርላቸው ዜጎች ምዝገባ መጀመሩን ነው ያሳወቁት። ለሥራ እድል መፍጠሪያነት የሚውለውን ሃብት የመለየት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም መምሪያ ኀላፊው ተናግረዋል።
በሕገ ወጥ መንገድ የተያዙ ሼዶችን ለማስመለስ መምሪያው በትኩረት እንደሚሠራም አመላክተዋል።
51 ሼዶች እና 40 ኮንቴነሮች ተይተው የማስመለስ ሥራ እየተከናወነ ስለመኾኑም አቶ ብዙዓየሁ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡- ዮናስ ታደሰ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!