በኦን ላይን ከአራት መቶ ሺ በላይ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን መስጠቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ።

41

ባሕርዳር፡ መስከረም 14/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከሐምሌ 1/2015 እስከ መስከረም 8/2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ 401 ሺ 830 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን በኦን ላይን መስጠቱን አስታውቋል። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከሐምሌ1/2015 ዓ.ም ጀምሮ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጡን በሀገር አቀፍ ደረጃ በኦን ላይን ማድረጉ ይታወሳል።

በዚህም ከፌደራል እስከ ክልል ባሉት የንግድ ተቋማትና መዋቅሮች 401 ሺ 830 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በኦን ላይን ተሰጥቷል። ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ ባወጣው መረጃ በኦንላይን ከተሰጡ የአገልግሎት የንግድ ምዝገባ፣ አዲስ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ እድሳት፣ የንግድ ሥራ ፈቃድ ስረዛ፣ የንግድ ስም ማሻሻያ እና ሌሎችም የሚገኙበት ሲሆኑ አገልግሎቱ በኦን ላይን በመሰጠቱ የተገልጋዮችን እንግልት ማስቀረት፣ ወጪ እና ጊዜያቸውንም በመቆጠብ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ተችሏል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleለመውሊድ በዓል የሚሰባሰብ ሁሉ የነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አሳሰበ፡፡
Next articleየአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች እና የሃይማኖት አባቶች መስቀል አደባባይን የማፅዳት ሥራ አከናወኑ ።