በበርሊን ማራቶን ትዕግሥት አሰፋ ክብረ ወሰን ሰበረች።

99

ባሕር ዳር: መስከረም 13/2015 ዓ.ም (አሚኮ)በበርሊን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግስት አሰፋ ክብረ ወሰኑን ሰበረች።

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግሥት ያሻሻለችው ክብረ ወሰን በብሪጅድ ኮስጊ በ2019 የችካጎ ማራቶን የተያዘውን ክብረ ወሰን ነው። ክብረ ወሰኑ 2 ሰዓት 14 ደቂቃ 04 ሰከንድ ነበር። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግሥት 2 ሰዓት 11 ደቂቃ 53 በመግባት ነው ክብረ ወሰኑን ያሻሻለችው። ትዕግሥት አሰፋ ክብረ ወሰን የሰበረችበት የማራቶን ውድድር በበርሊን ሁለተኛ ድሏ ኾኖ ተመዝግቧል።

በወንዶች የበርሊን ማራቶን ኢትዮጵያዊው አትሌት ታደሰ ታከለ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል። ኬኒያዊው አትሌት ኬፕቾጌ አንደኛ ደረጃን ይዞ አጠናቅቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleቅዱስ ጊዮርጊስ በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ከግብጹ አል አህሊ ጋር ይጫወታል።
Next article“የጉራጌ ማሕበረሰብ ባሕላዊና ታሪካዊ እሴቶች በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ ጥረት እየተደረ ነው” የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን