ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ትብብራቸውን ለማሳደግ ተስማሙ።

33

ባሕርዳር፡ መስከረም 12/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ አብዱላህ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር የሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

በውይይታቸው በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን ዘርፈ-ብዙ ትብብር ለማሳደግም ተስማምተዋል።

ሼክ አብዱላህ ቢን ዛይድ አል ናህያን በያዝነው የፈረንጆቹ አመት በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች በሚካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያን ሚና በተመለከተ ገለፃ ማድረጋቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

78ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በኒውዮርክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በአማራ ክልል ከመስኖ ልማት 40 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የሰብል ምርት ለማግኘት ታቅዷል” ግበርና ቢሮ
Next articleበኢትዮጵያ የታጠበ የድንጋይ ከሰልን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ለመቀነስ ከሁለት የሕንድ ኩባንያዎች ጋር ስምምነት ተፈረመ።