በዓባይ፣ በቆቃ እና በአዋሽ ተፋሰስ አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳሰበ፡፡

52

ባሕር ዳር: መስከረም 09/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በኢንስቲትዮቱ የትንበያ ባለሙያ ሳምራዊት አበበ በቀጣይ 10 ቀናት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጠንካራ የደመና ሽፋን እንደሚኖር ተናግረዋል፡፡

በዚህም በፀሐይ ብርሃን የታጀበ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የአየር ትንበያ መረጃ ያመላክታልም ነው ያሉት፡፡

በመሆኑም የአባይ፣ የቆቃ እና የአዋሽ ወንዞች በመሙላት ከተለመደው ፍሰታቸው ውጪ በመሆኑ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል በመሆኑ ሕዝቡ እንዲጠነቀቅ አሳስበዋል።

በከተሞችም ጎርፍ እንዳይከሰት የፈሳሽ ማስወገጃ ትቦዎችን ከቆሻሻ ማጽዳት እንደሚገባ ለፋብኮ ገልጸዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ከሚከናወኑ ተግባራት በተጓዳኝ ለግብርና ልማት በልዩ ትኩረት እየተሠራ ነው” ዶክተር ድረስ ሳህሉ
Next article“በሰሜን ጎንደር ዞን የዝናብ እጥረት በተከሰተባቸው ወረዳዎች 452 ሺህ ወገኖች ሰብአዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል” የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት