የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሳውዲ አረቢያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

60

ባሕርዳር፡ መስከረም 04/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሳውዲ አረቢያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በትምህርት እና ሥልጠና፣ የእግር ኳስ ልማት እና ትብብር ላይ ያተኮረ የመግባቢያ ስምምነት በሪያድ ተፈራርሟል።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጅራ እና የሳውዲ አቻቸው ያስር አል-ሚስሀል ናቸው።

የስምምነቱን ዝርዝር በቀጣይ እንደሚገለጽ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በማህበራዊ ትሥሥር ገጹ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።

ፌዴሬሽኑ ከዚህ ቀደም ከሞሮኮ ሮያል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር የትብብር ስምምነት ባሳለፍነው ዓመት በመፈራረም የጋራ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ተገልጿል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleፍቅረማርያም ያደሳ በኦሊምፒክ ቦክስ ማጣሪያ ሁለተኛ ኾኖ አጠናቀቀ።
Next article“ከመስከረም እስከ ታሕሳስ ወባ በከፍተኛ ኹኔታ የሚተላለፍበት በመኾኑ መከላከል ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት ይገባል” የአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት