
ባሕር ዳር: መስከረም 04/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ”ከዕዳ ወደ ምንዳ” በሚል መሪ መልእክት ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ መሪዎች የተዘጋጀ የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና በዛሬው ዕለት በአዳማ ከተማ ተጀምሯል።
የሥልጠናው አላማ ከፍተኛ መሪዎች ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ኹኔታዎችን ተገንዝበው ፤ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ፓርቲው ለሕዝቡ የገባውን ቃል ማስፈጸም የሚያስችል የአመራር አቅም እንዲፈጥር ያለመ መኾኑን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ ገልጸዋል።
በሥልጠናው ላይ ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ ከፍተኛ መሪዎች እየተሳተፉ መኾኑን ከፓርቲው የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!