ለዘመን መለወጫ በዓል የማዕከላዊ ጎንደር ዞን እና የጎንደር ከተማ አሥተዳድር በጥምረት የእርድ እንስሳት ስጦታ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አበረከቱ።

52

ጎንደር: ጳጉሜ 06/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አሥተዳደር እና የጎንደር ከተማ አሥተዳደር በጋራ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ በማሰባሰብ 19 የቀንድ ከብቶችን እንዲሁም ተጨማሪ በግና ፍየሎችን ለመከላከያ ሠራዊት አስረክበዋል።

የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሐይ ሕዝቡ በፀጥታ መዋቅሩ ያገኘው ሰላም ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማሰብ ስጦታው ለሀገር መከላከያ ሠራዊት መበርከቱን ተናግረዋል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አላምረው አበራ ለአዲስ ዓመት ለመከላከያ ሠራዊት ያለንን ድጋፍ ለማሳየት እገዛ መደረጉን ገልጸዋል።

በርክክቡ ወቅት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት የተገኙት ብርጋዴል ጄኔራል ማርየ በየነ ሠራዊቱ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት የሕዝብ ድጋፍ ወሳኝ ነው ብለው ለተደረገው እገዛ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።

ዘጋቢ:- ምሥጋናው ከፍያለው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ለመከላከያ ሠራዊት አባላትና ሌሎች የጸጥታ ኃይሎች ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሰንጋዎችንና ፍየሎችን አበረከተ።
Next article“ባሕረ ሃሳብ፡ ባሕር ስንል ዘመን፤ ሃሳብ ስንል ሥሌት ማለታችን ነው” መምህር ማዕበል ፈጠነ