የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ በመግለጫቸው ያነሷቸው አንኳር ነጥቦች፦

47

👉 በአማራ ክልል የተፈጠረውን የሰላም እጦት ለመፍታት በተሠሩ ሥራዎች አንፃራዊ ሰላም እየተፈጠረ ነው።
👉የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ በርካታ ታጣቂዎች ተፈጥረዋል፤ ታጣቂዎቹ ወደ መደበኛ ሕይወት እንዲመለሱ ፣ በመንግሥት የፀጥታ መዋቅር እንዲካተቱ ብዙ ሥራ ተሠርቷል።

👉 አስቸኳይ ጊዜ በመታወጁና በቅንጅት በመሠራቱ በክልሉ አንፃራዊ ሰላም ተፈጥሯል።
👉 ሕዝቡ ሰላም በመፈለጉና ጦርነትን በመሰልቸቱ ክልሉ በፍጥነት ወደ ሰላም ተመልሷል።
👉 የአማራ ሕዝብ ሰላም እንዲቀጥል ፤ ግጭት እንዲቆም የተሠራው ሥራ ታሪክ የማይረሳው ፤ የአማራን ሕዝብ ሥነ ልቦና የሚመጥን ነው።

👉ሕዝቡ የጀመረውን የሰላም ሥራ አጠናክሮ ከሄደ በአጭር ጊዜ ወደ ፍጹም ሰላም መመለስ ይቻላልም ነው ያሉት።
👉 ፖለቲከኞችም ኾነ ሌሎች አካላት ለዜጎች ሰላም መሥራት እና ከአባባሽ ነገሮች መራቅ አለባቸው።
👉 መጀመሪያችንም መጨረሻችንም የሕዝብ ሰላም መኾን አለበት። አሁን ላይ ክልሉ ከችግር እየወጣ ነው።
👉 የአማራ ሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ በዲሞክራሲ አግባብ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር መታገል አለበት።

👉 ክልሉን የሚመጥን የሕዝቡን ሥነ ልቦና እያየ ጥያቄዎችን መመለስ የሚያስችል መሪ ማደራጀት ስላስፈለገ ከክልሉ ጀምሮ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ መሪዎችን የማደራጀት ሥራ እየተሠራ ነው።

👉ከሕዝብ ጋር መግባባትና በሁሉም ነገር ሕዝብን ባለቤት ማድረግ ወሳኝ በመኾኑ ከሕዝብ ጋር መወያየት ፣ በግልፅ መነጋገርና መግባባት ያስፈልጋል።

👉 የተፈጠረው አለመረጋጋት የአማራን ሕዝብ አይመጥንም፤ የአማራ ሕዝብ ከግጭት ወጥቶ የተጠማውን ልማት ማግኘት አለበት።

👉 ወደ ልማት ሳይገባ ኢኮኖሚን ማሳደግ ሳይቻል ጥያቄዎችን መመለስ አይቻልም። ለአማራ ሕዝብ የተጠማውን ልማት መስጠት ግድ ይላል።

👉 ሕዝቡን እያማረሩ ያሉ የመልካም አሥተዳደር ችግሮች መፈታት አለባቸው። መፍታት ሲገባን ያልፈታናቸው ችግሮች እየበዙ በመምጣታቸው ሕዝቡ ተቀይሞናል። ከላይ እስከታች ያለው መዋቅር ከጥላቻ ነፃ ኾኖ ለአካባቢው ሰላምና ልማት መጨነቅ ፣ የሕዝብ እንባ ማበስ አለበት።

👉መፍታት የሚገባንን ሳንፈታ ከሄድን ሕዝብን እያስቀየምን እንሄዳለን፣ ሕዝብ ሲቀየም ደግሞ ለአመራር እንቸገራለን። አዳዲስ መሪዎችም ኾኑ በሕዝብ ታምኖባቸው የሚቀጥሉ መሪዎች ለሕዝብ ጥቅም መሥራት አለባቸው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሰማያዊ ካልኾነ በስተቀር ምድራዊ ሰው ይሄን ሥራ እንደማያስተወኝ አምናለሁ፡፡” ብርሃን መልካሙ
Next articleርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ልዩ ልዩ ሹመቶችን የሰጡ።