ዛሬ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር ትጫወታለች።

49

ባሕር ዳር: ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ዛሬ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ትጫወታለች።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት ለሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታውን ዛሬ ከግብጽ ጋር ያደርጋል።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ በካይሮ ‘ሰኔ 30 ስታዲዬም’ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ ይከናወናል።

በጊዜያዊ ዋና አሠልጣኝ ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለጨዋታው ከነሐሴ 23 እስከ 28/2015 በአዲስ አበባ ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሀገራዊ ምክክሩ የተረጋጋችና የምንፈልጋትን ጠንካራ ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ መደላድል ለመፍጠር አጋዥ እንደሚሆን ትልቅ እምነት አለን” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
Next article“ሰውን ለመርዳት ሰው መኾን በቂ ነው” የሜቄዶንያ መሥራች ቢኒያም በለጠ