የአማራ ክልል የጸጥታ ምክር ቤት በክልሉ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ ዙሪያ እየመከረ ነው።

112

ባሕር ዳር: ነሐሴ 27/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ከክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት አባላት ጋር ምክክር እያካሄዱ ነው።

የክልሉ የጸጥታ አደረጃጀት በክልል ደረጃ አዲስ መዋቅር መሥራቱን ተከትሎ አደረጃጀቱ በፍጥነት እስከ ታችኛው አካል ድረስ ይወርዳል ተብሏል።

በክልል ደረጃ የተካሄደው የጸጥታ አደረጃጀት የክልሉን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻ እና የማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል። አደረጃጀቱን እሰከ ከታችኛው መዋቅር ድረስ በፍጥነት ማውረድ ያስፈልጋል ተብሏል።

ከአደረጃጀቱ ጎን ለጎን የክልሉን ሰላም በአጭር ጊዜ ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ እየተሠራ እንደሆንም ተነስቷል። የክልሉ የጸጥታ መዋቅር የሕዝብን ጸጥታ የሚያውኩ ችግሮችን በመለየት በፍጥነት መሥራት እንዳለበትም ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አንስተዋል።

ፈጥኖ ወደ ሥራ መግባት እና አሁን ያለውን የጸጥታ ሥራ ማገዝ በሂደትም ተክቶ መሥራት የቀጣይ ጊዜ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑ አጽንኦት ተሰጥቶት በውይይቱ ተነስቷል።

ዘጋቢ፦ ታዘብ አራጋው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏ ከብራዚል ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት ለማጠናከር ዕድል ይፈጥራል” አምባሳደር ዣንዲር ፌሔይራ ዶስ ሳንቶስ
Next articleበደብረ ሲና ከተማ የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል በትብብርና በጋራ መሥራት እንደሚያስፈልግ ብርጋዴር ጀኔራል እሸቱ መንግሥቴ አሳሰቡ።