በቡዳፔስቱ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ለተሳተፈው ልዑካን ቡድን ነገ አቀባበል እንደሚደረግ ባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

30

ባሕር ዳር: ነሐሴ 22/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በ19ኛዉ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በቡዳፔስት ለተሳተፈው ልዑካን ቡድን ነገ አቀባበል እንደሚደረግ የባሕልና ስፖርት ሚኒስትሩ ቀጀላ መርዳሳ ገለጸዋል፡፡

የቡዳፔስት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና ኢትዮጵያ ጥሩ ውጤት ያገኘችበት እንደነበርም ተናግረዋል ። 2 ወርቅ ፣ 4ብርና 3 ነሃስ ሜዳሊያዎች ማገኘቷንም በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡

የተገኘው ውጤት የኢትዮጵያን ገፅታ የገነባ በመኾኑ ለመላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ለአትሌቲክስ ልዑኩ ነገ ነሐሴ 23/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል እንደሚደረግም ነው የተናገሩት። እስከ 2 ሰዓት ከሚደረገውን አቀባበል ቀጥሎ አትሌቶቹ በአውራ ጎዳናዎች በመዘዋወር ከሕዝቡ ጋር ደስታቸውን እንደሚገልጹም ተመልክቷል።

ዘጋቢ:- አሚናዳብ አራጋው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበኩር ጋዜጣ ነሐሴ 22/2015 ዓ.ም ዕትም
Next articleኢትዮጵያ በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 6ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች።