“የአማራ ክልል ከገባበት ችግር ወጥቶ ለሀገር ምሳሌ እንደሚኾን እተማመናለሁ” አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ

114

ባሕር ዳር: ነሐሴ 20/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር በዓለ ሲመት በባሕርዳር ከተማ ተካሂዷል። በበዓለ ሲመቱ ላይ የተገኙት የሶማሌ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሙስጠፌ ሙሐመድ አዲስ ለተሾሙት መሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

በአስቸጋሪ ወቅት ክልሉን ለመሩት ለቀድሞው ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ምሥጋና አቅርበዋል።
በአማራ ክልል የተፈጠረው ችግር በአጭር ጊዜ መሻሻል በማሳያቱ የተሰማቸውን ደስታም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ከገባበት ችግር ወጥቶ ለሀገር ምሳሌ እንደሚኾን እተማመናለሁ ነው ያሉት። የሶማሌ ክልል ከአማራ ክልል ጎን መኾኑንም ገልጸዋል።

ዘጋቢ:- ታርቆ ክንዴ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የአማራ ችግር የአፋር ችግር ነው፤ አማራ የሰውነታችን አንድ አካል ነው” አቶ አወል አርባ
Next article“አዲሶቹ መሪዎች የተቀበሉት ኃላፊነት የአማራ ሊሂቃንን እና የመላውን የአማራን ሕዝብ እገዛ የሚጠይቅ ነው” አቶ ደስታ ሌዳሞ