የክልል ርእሳነ መሥተዳድሮች በአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር በዓለ ሲመት ለመታደም ባሕርዳር ገቡ።

356

ባሕር ዳር: ነሐሴ 20/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የክልል ርእሳነ መሥተዳድሮች በአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር በዓለ ሲመት ለመታደም ባሕርዳር ገብተዋል። ርእሳነ መሥተዳድሮቹን የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተሰፋዬና የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። የአማራ ክልል ምክር ቤት ትናንት ነሐሴ 19/2015 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ጉባዔ የቀድሞውን ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) የመልቀቂያ ጥያቄ ተቀብሎ አቶ አረጋ ከበደን ርእሰ መሥተዳድር አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።

ትናንት የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሆነው የተሾሙት አረጋ ከበደ በዓለ ሲመት ዛሬ በባሕር ዳር ይካሄዳል።
ርእሳነ መሥተዳድሮች ባሕር ዳር የገቡት በአዲሱ ርእሰ መሥተዳድር በዓለ ሲመትና የሥራ ርክክብ ለመታደም ነው።

ዘጋቢ:- ታርቆ ክንዴ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ሁለት ልዩ ልዩ ሹመቶችን ሰጡ።
Next articleየአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በዓለ ሲመት እየተካሄደ ነው።