“ኢትዮጵያ የተትረፈረፈ የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ አቅም ባለቤት ናት።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)

54

ባሕር ዳር: ነሃሴ 13/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት “ከወንድሜ ሼክ ሙሀመድ ቢን ዛይድ ጋር የከፈትነው የሳይንስ ሙዚየም አውደ ርዕይ የሀገራችንን ከፍተኛ የውሃ እና የኢነርጂ አቅም ያሳያል!” ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም የውሃ እና ኢነርጂ አውደ ርዕይ በይፋ ከፍተዋል።

የኢትዮጵያን የውኃ እና የኢነርጂ ሀብቶች እንዲሁም እምቅ አቅምን ለማሳየት ያለመው አውደ ርዕይ ለሚቀጥሉት ሳምንታት ለሕዝብ ክፍት ይሆናል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleኅብረተሰቡ ለሰላም ዘብ እንዲቆም ፖሊስ ጠየቀ።
Next article“ተግባብተንና ተናበን የከተማችንን ሰላም መጠበቅ ይገባናል” የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የሚሊሻ አባላት።