አቶ ወርቁ አይተነው በሞጣ ከተማ አስተዳደር ከሰሞኑ የተቃጠሉ ቤተ እምቶችን መልሶ ለመገንባት የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ቃል ገቡ፡፡

869

አቶ ወርቁ አይተነው በሞጣ ከተማ አስተዳደር ከሰሞኑ የተቃጠሉ ቤተ እምቶችን መልሶ ለመገንባት የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ቃል ገቡ፡፡

በምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ አስተዳደር መስጂዶች፣ ሱቆችና ቤተ ክርስቲያን ላይ ቃጠሎ መድረሱ ይታወሳል፡፡ የእምነት ተቋሟቱን መልሶ ለመገንባትም እንቅስቃሴ መጀመሩም የሚታወስ ነው፡፡

የእምነት ተቋማቱ ላይ የደረውን ጉዳት ዛሬ በሞጣ ተገኝተው የጎበኙት ባለሀብት አቶ ወርቁ ዓይተነው ለመልሶ ግንባታ የሚውል የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ቀል መግባታቸውን ከሞጣ ከተማ አስተዳደር እና የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴው ያኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ዝርዝር የድጋፍ አሰባበስ ሁኔታው ያለበትን ደረጃ በተመለከተ ከሰሞኑ መረጃ የምናደርስ ይሆናል፡፡

Previous articleበኩር ጋዜጣ ታኅሳስ 20-2012 ዓ/ም
Next articleበዋሽንግተን ዲሲ የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) አደረጃጀት ተቋቋመ፡፡