በሕግ አግባብ መሠረት የክልሉ የጸጥታ መዋቅር እና የመከላከያ ሠራዊት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እየተሠራ መኾኑን ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ገለጹ።

126

ባሕር ዳር: ሐምሌ 26/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) በመግለጫቸው ስለጸጥታ አካላት ያነሷቸው ነጥቦች፦

👉በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የጸጥታ ችግሮች ተፈጥረዋል።

👉የጸጥታ ችግሩ የሰውን እንቅስቃሴ እየገታ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደረ መኾኑን ነው ያነሱት፡፡

👉በግጭቱ በክልሉ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ የኾነ ሰብአዊ ኪሳራ እያጋጠመ መኾኑንም አንስተዋል፡፡

👉የጸጥታ ችግር ሲያጋጥም የክልሉ የጸጥታ መዋቅርና የመከላከያ ሠራዊት ሕግ የማስከበር ተልእኮን እንደሚወጣ በየትኛውም ሀገርና መንግሥት የታወቀ መኾኑንም አንስተዋል፡፡

👉በሕግ አግባብ መሠረት የክልሉ የጸጥታ መዋቅር እና የመከላከያ ሠራዊት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እየሠራ ይገኛል፡፡

👉የጸጥታ መዋቅሩ እንቅስቃሴ የሕዝብን ጥቅም ለማስጠበቅ እና የሕግ የበላይነትን ለማስከበር ነው፡፡

👉 በመከላከያ ሠራዊት ላይ ያልተገባ ስም መስጠት እና መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ መንዛት አስነዋሪ መኾኑን ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡

👉የክልሉ የጸጥታ መዋቅርም ኾነ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ሉዓላዊነትን ለማስከበርና የሀገር አንድነትን ለማስጠበቅ ምሰሷችን ነው፡፡

👉የመከላከያ ሠራዊት ከሁሉም የሀገራችን ሕዝቦች የተውጣጣ፣ ሀገራዊ ቁመና ያለው ተቋም ነው።

👉የመከላከያ ሠራዊት ተቋም መመኪያችን በመኾኑ መደገፍና ማበረታታት ይገባል፡፡

👉የክልሉ የጸጥታ ኀይልም ኾነ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ወደ ተለያየ አካባቢ ሲንቀሳቀስ መተንኮስ ተገቢም ኾነ ሕጋዊ አለመኾኑን ገልጸዋል፡፡

👉 የክልሉ የጸጥታ መዋቅር እና መከላከያ ሠራዊት ሕግ ለማስከበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሁሉም የክልሉ ሕዝብ ከጎኑ በመኾን የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ታርቆ ክንዴ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ ከአሜሪካ ግምጃ ቤት ምክትል ረዳት ጸሐፊ ጋር ተወያዩ ።
Next articleሁሉም በየአካባቢው ያለውን ትንኮሳ በአስቸኳይ በማስቆም ወደ ሰላማዊ ውይይትና ምክክር እንዲመለስ ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ጥሪ አቀረቡ።