“ኢትዮጵያ ትልቅ አቅም ያላት ሀገር ብቻ ሳትኾን በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች መዋእለ ነዋይ ለማፍሰስ ለሚሹ ሁሉ ምቹ ኹኔታን እየፈጠረች ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

73

ባሕር ዳር: ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም (አሚኮ)

ኢትዮጵያ ለብዙ ሺህዎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የሥራ እድል ያስገኙ 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ገንብታ ወደ ሥራ አስገብታለች። የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮችንም ገንብተን በሥራ ላይ እንገኛለን ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር በመኾን ዛሬ ጠዋት በአንደኛው የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በምርት ሥራ ላይ ካሉ ኢንዱስትሪዎቻችን ሁለቱን አብረን ጎብኝተናል ነው ያሉት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት ኢትዮጵያ ትልቅ አቅም ያላት ሀገር ብቻ ሳትኾን በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች መዋእለ ነዋይ ለማፍሰስ ለሚሹ ሁሉ ምቹ ኹኔታን እየፈጠረች ነው ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና አጀማመርን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተዘዋውረው ተመለከቱ።
Next articleበአማራ ክልል ከሚገኘው 18 ሚሊዮን በላይ የተበጣጠሰ ማሳ ውስጥ 70 በመቶ የካዳስተር ሥራ መሥራቱን የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ገለጸ።