እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን እየተቀበለ ነው።

47

ባሕር ዳር: ሐምሌ 23/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የሁለተኛ ዙር የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን በዛሬው እለት መቀበል መጀመሩን እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል።

በዚህ ዙር ከ6 ሺ 500 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን የሚወስዱ ሲሆን በነገው እለት አጠቃላይ ገለጻ ተደርጎ ከማክሰኞ ጀምሮ ፈተናው የሚሰጥ ይሆናል።

ዩኒቨርሲቲው ለተፈታኝ ተማሪዎች መልካም ውጤት ተመኝቷል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ትንሽ ሥጋ እንደ መርፌ ትወጋ”
Next article“ሕዝብን ለማገልገል የሥራ ድንበር የለውም” ኢብራሂም ሙሐመድ (ዶ.ር)