“የተፌ ወንዝ ድልድይ ሕይወትን የታደገ፤ ሁለንተናዊ የእለት ተእለት እንቅስቃሴን ክረምት ከበጋ የሚያስቀጥል ነው” አቶ ሙሐመድ ያሲን

42

ባሕር ዳር: ሐምሌ 17/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሐመድ ያሲን በተፌ ወንዝ የመሻገሪያ ድልድይ ባለመገንባቱ እናትን ከልጇ የነጠለ፤ ልጅን ካለአባት ያስቀረ፤ ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው የገታ፤ ማኅበረሰቡን ለከፍተኛ እንግልት የዳረገ ክስተት ላይደገም ዛሬ ላይ ፋይሉ ተዘግቷል ብለዋል።

እነሆ በዛሬው እለት በምስራቅ ጎጃም ዞን ሰዴ ወረዳ ባለፉት ወራት ወደ ሥራ የገባው የተፌ ወንዝ ኮንክሪት ድልድይ ግንባታው ተጠናቆ በዚህ መልኩ መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ነው ያሉት።

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የሰዴ ወረዳ ማኅበረሰብ ልማትን ከመጠየቅ ባለፈ የራስን አቅም በማስተባበር እየሠሩት ያለው የመንገድ ግንባታና ጥገና ሥራ እንዲሁም ልዩ ልዩ ስትራክቸር ግንባታ በተሞክሮነት የሚወሰድና እንዲሰፋ የሚደረግ ተግባር ነው ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የተፌ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።
Next articleበባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፕሮፌሰሮች ወግ የተሰኘ መርሃ ግብር ተካሄደ።