በአንድ ቀን ከ2 መቶ በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ-ግብር በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

38

ባሕር ዳር: ሐምሌ 17/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ከደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ከአራቱም ክፍለ ከተማ የተወጣጡ ከ2 መቶ በላይ የክረምት በጎ ፈቃድ ሰጭ ወጣቶች የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ-ግብር በንጉስ ተክለ- ሃይማኖት አደባባይ እየተካሄደ ነው፡፡

የከተማ አሥተዳደሩ ወጣቶች እና ሴቶች ሊግ ከደብረ ማርቆስ ከተማ ደም ባንክ አገልግሎት ጋር በጋራ ባዘጋጁት የደም ልገሳ መርሃ-ግብር በአንድ ቀን ሁለት መቶ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መኾኑን የከተማ አሥተዳደሩ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ያጋጠሙና ሊያጋጥሙ የሚችሉ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ችግሮችን ለመፍታት መረጃንና ማስረጃን መሠረት ያደረገ ተግባር እና ውሳኔ ማድረግ ያስፈልጋል“ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር
Next article20 ሺህ 411 ነጥብ 5 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ ተጓጓዘ።